በያኔት ኮሌጅ ሰፈረ ሰላም ካምፓስ ሲሰጥ የቆየው ይህ ስልጠና በያኔት ኮሌጅ ከአርሲ ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ በመተባበር ያዘጋጁት ስልጠና ሲሆን ስልጠናው ላለፉት ሦስት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ ቆይቶ በዛሬዉ ዕለት በይፋ ተጠናቅቋል፡፡ ስልጠናውን የተካፈሉት የያኔት ኮሌጅ መምህራን ሲሆኑ መምህራን እያንዳንዳቸው በሰለጠኑት ስልጠና መሰረት ተማሪዎችን እንደሚያሰለጥኑ ሥልጠናውን ያዘጋጁት አካላት ገልጸዋል ፡፡
በስልጠናው መዝጊያ ላይ ለሰልጣኞቹ የምስክር ወረቀት የሰጡት ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ደሱ ሲሆኑ ለስልጠናው ፍሬያማነት የመምህራኖቹ ሚና እጅግ ጉልህ መሆኑን በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ ተገልጿል፡፡
